በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
የእመቤታችን ወዳጆች ሆይ እንኳን ለንጽሕተ ንጹሐን ለቅድስተ ቅዱሳን ለድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ፅዮን ማርያም (አክሱም ፅዮን ) ታላቅ ክብረ በዓል በሰላም አደረሰን ! አደረሳችሁ!
ወበዛቲ እለት ህዳር 21 ቀን የእስራኤላውያን መመኪያ በእመቤታችን ስም የተሰየመችው ታቦተ ጽዮን ዳጐን በተባለው ጣኦት ላይ ኃይሏን ክብሯን የገለጸችበት ቀን ነው::
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በመፅሐፍ ቅዱስ በጥቂቱ
 + "ጽዮንን ክበቡአት፥ በዙሪያዋም ተመላለሱ ፥ ግንቦችዋንም ቅጠሩ" መዝ 48:12
 + "ሰው ሁሉ እናታችን ጽዮን ይላል፥ ከውስቶም ሰው ተወልዶባታል።" መዝ 68:15
 + "በአንቺ የሚኖሩ ሁሉ ደስተኞች ናችው።" መዝ 86:7
 + "እነሆም ፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል" የሉቃስ ወንጌል 1:48
 + "እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦታልና ማደራያውም ትሆነው ዘንድ ወዶታልና። ይቺ የዘላለም ማረፊያዬ ናት መርጫታለሁና በዚችም አድራለሁ።" መዝ 131: 12-14
 + "ታላቅ ምልክት በሰማይ ታየ ፀሀይ ተጎናፅፋ ጨረቃ በእግሮቿ በኩል ያላት በራሶ ላይ አስራ ሁለት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች" ራዕ፡ዮሐ 12:1-3
 + "ለአንቺም የማይገዛ ሕዝብና መንግሥት ይጠፋል ፥ እነዚያ አሕዛብም ፈጽመው ይጠፋሉ።ኢሳይያስ 60፤12
 + "በወርቅ ልብስ ተጎናስፅፋና ተሸፋፍና ንግስቲቱ በቀኝህት ቆማለች። ልጄ ሆይ ስሚ ጆሮሽንም ኣዘንብይ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ ንጉስ ውበትሽን ወዷልና እርሱም ጌታሽ ነው። የምድር ባለጠጎች አህዛብ በፊትሽ ይማለላሉ።" መዝ 44/45 : 9-10
 + "በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ። በምድር ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚአቸዋለሽ። ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ ስለዚህ ለአለምና ለዘላለም አህዛብ ይገዙልሀል።" መዝ 44 : 12-14
 + "ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።" ትንቢተኢሳይያስ 7:14
 + "በገነቱ የምትቀመጪ ሆይ፥ ባልንጀሮች የአንቺን ቃል ያደምጣሉ፤ ቃልሽን አሰሚኝ። መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን 8:13"
 + "እግዚአብሔር ዘር ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንን እንደ ገሞራም በመሰልን ነበር።" ትንቢተ ኢሳያስ 1-9
...............................................................................................
ድንግል ሆይ በቤተ ልሔም ካንቺ የተለደውን መወለድ በጨርቅ የተጠቀለለውንም አድግና ለህም በብርድ ወራት እስትንፋስን ያሟሟቁትንም አሳስቢ፡፡ ድንግል ሆይ ርጉም በሆነ በሄርድስ ዘመን ከርሱ ጋራ ከሀገር ስትሸሺ ከአንቺ ጋራ ወሰደዱን አሳስቢ፡፡ ድንግል ሆይ ከዕይኖችሽ የፈሰሰውንና በተወደደ ልጅሽ ፊት የወረደውን መሪር እንባ አሳስቢ፡፡ ድንግል ሆይ ርኃቡንና ጥሙን ችግሩንና ኃዘኑን ከእርሱ ጋር የደረሰብሽንም ጭንቅ ሁሉ አሳስቢ፡፡ ጥፋትን ያይደለ ይቅርታን አሳስቢ መዓትን ያይደለ ምሕረትን አሳስቢ ለጻድቃን ያይደለ ለኃጥእን አሳስቢ፤ ለንጹሐን ያይደለ ለተዳደፍት አሳስቢ፡፡
የልመናዋ ክብር ፍጹም የሆነ፤ የረድኤትዋ ሀብት ጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚመላ፤ የተወደደ የልጅዋ ቸርነት በእውነት ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡ አሜን!!!

አስተያየቶች